
- Administrator
- Projects
- Hits: 673
ለጌጃ የልማት ተነሺዎች ገንብተን ባስረከብናቸው ሱቆች የንግድ ሥራዎች ተጀምረዋል
- Administrator
- Projects
- Hits: 673
ለጌጃ የልማት ተነሺዎች ገንብተን ባስረከብናቸው ሱቆች የንግድ ሥራዎች ተጀምረዋል
ብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን በገነባቸው በእነዚህ ሱቆች አማካይነት፣ በልማት ተነሺ ከሆኑት የኅብረተሰብ ክፍሎች በተጨማሪ በአከባቢው በጉልት ሥራ ይተዳደሩ የነበሩ እናቶችም ባለ ሱቅ እንዲሆኑ ተደርጓል።
ለአከባቢው ነዋሪዎች የተለያዩ ሸቀጣ ሸቀጦች፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ የአዋቂና የሕጻናት አልባሳት፣ የፕላሰቲክ ውጤቶችን በማቅረብና የልብስ ስፌት አግልግሎት እየሰጡ ራሳቸውንና የአከባቢውን ነዋሪዎች እየጠቀሙ ይገኛሉ። የእነዚህ 10 ሱቆች መገንባት በአከባቢው ይኖሩ የነበሩ ሴቶችና አቅመ ደካሞች በንግድ ሥራ ተሰማርተው ራሳቸውን እንዲችሉ አስችሏል። ፋውንዴሽኑ በጠቅላላው 1.5 ሚሊዮን ብር ወጪ አድርጎ ሱቆቹን አስገንብቶ ለልደታ ከተማ ክፍለ ከተማ ማስረከቡ ይታወሳል።